በፊሊፒንስ የተከሰተው የ7.8 ማግኒቲዩድ የመሬት መንቀጥቀጥ የ15 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ

በፊሊፒንስ በሚገኘው ሚንዳናኦ ደሴት ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የተከሰተውን የሬክተር ስኬል መጠኑ 7.8 የሆነውን ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ የሟቾች ቁጥር ቢያንስ ወደ 15 ማደጉን የሀገሪቱ የአደጋ ስጋት አመራር ባለስልጣናት አስታውቀዋል። 

Jun 8, 2026 - 15:51
 0  6
በፊሊፒንስ የተከሰተው የ7.8 ማግኒቲዩድ የመሬት መንቀጥቀጥ የ15 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ

በፊሊፒንስ በሚገኘው ሚንዳናኦ ደሴት ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የተከሰተውን የሬክተር ስኬል መጠኑ 7.8 የሆነውን ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ የሟቾች ቁጥር ቢያንስ ወደ 15 ማደጉን የሀገሪቱ የአደጋ ስጋት አመራር ባለስልጣናት አስታውቀዋል። 

በጄኔራል ሳንቶስ ከተማና አካባቢው በደረሰው በዚህ አደጋ ከ100 በላይ ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ በርካታ ህንጻዎች ሙሉ በሙሉ መደርመሳቸውን የሚያሳዩ ምስሎችና ቪዲዮዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጩ ይገኛሉ።

ከመጀመሪያው ጠንካራ ንዝረት በኋላ እስከ 6.5 የሬክተር ስኬል የሚደርሱ ተከታታይ የድንገተኛ አደጋዎች ያጋጠሙ ሲሆን፣ በባህር ዳርቻ አካባቢዎች ላይም የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ተጥሏል።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ፌርዲናንድ ማርኮስ ጁኒየር በክልሉ አስቸኳይ የነፍስ አድንና የረድኤት ስራዎች እንዲከናወኑ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

What's Your Reaction?

like

dislike

love

funny

angry

sad

wow