ኔታንያሁ እስራኤል በሊባኖስ የያዘችውን መሬት እንደማትለቅ አስታወቁ
በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረስም፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሀገራቸው በሊባኖስና በሶሪያ ግዛት ላይ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንደምትቀጥል ቃል ገብተዋል።
በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረስም፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሀገራቸው በሊባኖስና በሶሪያ ግዛት ላይ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንደምትቀጥል ቃል ገብተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የእስራኤል ጦር በሊባኖስ ውስጥ መቆየቱን እንደሚቀጥልና 570 ካሬ ኪሎ ሜትር አካባቢን ይዞ እንደሚቆይ ያመለከቱ ሲሆን፣ በአገሪቱ የጸጥታ መከላከያ ቀጠና ውስጥም አስፈላጊ እስከሆነ ድረስ እንደሚቆዩ አስታውቀዋል።
ስምምነቱን ያስታወቁት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼባዝ ሻሪፍ በበኩላቸው፣ የመግባቢያ ሰነዱ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የሚደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን በቋሚነት ማቋረጥን እንደሚያካትት ገልጸው እስራኤል በኢራን ከሚደገፈው የሊባኖስ ታጣቂ ሂዝቦላህ ጋር እ.ኤ.አ. ከጥቅምት 2023 ጀምሮ በጦርነት ውስጥ የገባች ሲሆን፣ በጥቅምት 2024 ደግሞ ድንበር ተሻጋሪ ወረራዎችን የጀመረች ሲሆን በዚህ ግጭትም እስካሁን በጣም ብዙ ሰዎች ተገድለዋል።
What's Your Reaction?