ታሪካዊው የሰላም ስምምነት እና የኢራን እግር ኳስ ቡድን ወደ አሜሪካ ገባ

በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ወታደራዊ ግጭት ለማስቆም የሚያስችል የሰላም ስምምነት መታወጁን ተከትሎ፣ የኢራን ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለአለም ዋንጫ ውድድር አሜሪካ ገብቷል። ቡድኑ በሎስ አንጀለስ ከተማ ያረፈው፣ ሁለቱ ሀገራት ጦርነቱን ለማቆም የደረሱበት የሰላም ውል ይፋ ከተደረ በኋላ ነው።

Jun 15, 2026 - 13:10
 0  5
ታሪካዊው የሰላም ስምምነት እና የኢራን እግር ኳስ ቡድን ወደ አሜሪካ ገባ


በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ወታደራዊ ግጭት ለማስቆም የሚያስችል የሰላም ስምምነት መታወጁን ተከትሎ፣ የኢራን ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለአለም ዋንጫ ውድድር አሜሪካ ገብቷል። ቡድኑ በሎስ አንጀለስ ከተማ ያረፈው፣ ሁለቱ ሀገራት ጦርነቱን ለማቆም የደረሱበት የሰላም ውል ይፋ ከተደረ በኋላ ነው።

ይህ ታሪካዊ ስምምነት የተሰማው፣ የኢራን ብሔራዊ ቡድን በሎስ አንጀለስ ከኒውዚላንድ ጋር የሚያደርገው የመክፈቻ የአለም ዋንጫ ጨዋታ ሊጀመር አንድ ቀን ሲቀረው መሆኑ ደግሞ ክስተቱን ልዩ ያደርገዋል።

የኢራን ብሔራዊ ቡድን አጥቂ መህዲ ታሬሚ እንደተናገረው፣ ቡድኑ አሜሪካ ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ የነበረው ከፍተኛ የፖለቲካ ውጥረት በውድድሩ ዝግጅት ላይ ጥላ ጥሎበት ቆይቷል። በነበረው አለመረጋጋት ምክንያት የቡድኑ የዝግጅት ሂደት ተስተጓጉሎ የነበረ ሲሆን፣ በተለይም የቪዛ ችግር አጋጥሟቸው የአለም ዋንጫ የልምምድ ካምፓቸውን ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ተገድደው እንደነበር አስታውሷል።

የስምምነቱ መረጃ የሰጡት የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሻሪፍ እንዳስታወቁት፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተደረሰው ይህ ስምምነት ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ረገድ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ሙሉ በሙሉ የሚያቆም ነው።
ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት በቀጣዩ አርብ በስዊዘርላንድ ውስጥ በይፋ ፊርማውን እንደሚያኖርም የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር አረጋግጠዋል።

What's Your Reaction?

like

dislike

love

funny

angry

sad

wow