የአሜሪካና ኢራን ስምምነት የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ እንዲያሽቆለቁል አደረገ
የዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያን ለወራት ሲያናውጥ የነበረው የአሜሪካና ኢራን ውጥረት መርገብን ተከትሎ፣ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል
የዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያን ለወራት ሲያናውጥ የነበረው የአሜሪካና ኢራን ውጥረት መርገብን ተከትሎ፣ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል። ሁለቱ ሀገራት ግጭቱን ለማስቆምና ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ የባህር መስመር በድጋሚ ለመክፈት የሚያስችል ጊዜያዊ ስምምነት መፈራረማቸውን ተዘግቧል።
ይህ ስምምነት በዓለም አቀፉ የነዳጅ አቅርቦት ላይ ተጋርጦ የነበረውን ስጋት በእጅጉ ያቀለለው ሲሆን፣ በዚህም ሳቢያ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል ወደ 78.66 ዶላር ዝቅ ብሏል። በተመሳሳይ መልኩ የዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዲየት (WTI) የነዳጅ ዋጋም ቅናሽ አሳይቶ በበርሜል 75.81 ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል።
What's Your Reaction?