የ40/60 እና የካፒታል ፕሮጀክት የንግድ ቤቶች ውል ማጠናቀቂያ ጊዜ ተራዘመ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ8ኛ ዙር (40/60) እና በ2ኛ ዙር (ካፒታል ፕሮጀክት) የንግድ ቤቶች ግልጽ ጨረታ አንደኛ ለወጡ አሸናፊዎች የነበረውን የውል ማፈጸሚያ ጊዜ ለተጨማሪ 5 ተከታይ የሥራ ቀናት ማራዘሙን አስታወቀ።

Jun 15, 2026 - 16:01
Jun 15, 2026 - 16:27
 0  5
የ40/60 እና የካፒታል ፕሮጀክት የንግድ ቤቶች ውል ማጠናቀቂያ ጊዜ ተራዘመ



የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ8ኛ ዙር (40/60) እና በ2ኛ ዙር (ካፒታል ፕሮጀክት) የንግድ ቤቶች ግልጽ ጨረታ አንደኛ ለወጡ አሸናፊዎች የነበረውን የውል ማፈጸሚያ ጊዜ ለተጨማሪ 5 ተከታይ የሥራ ቀናት ማራዘሙን አስታወቀ።

በሂደቱ ላይ የቴክኒክ መስተጓጎል በመፈጠሩ፣ ከተጫራቾች የገንዘብ ዝውውር ጋር የተያያዙ ችግሮችን ታሳቢ በማድረግና፣ የባከኑ የሥራ ቀናትን ለመተካት እንደሆነ ተገልጿል።

አዲሱ የውል ማስፈጸሚያ ጊዜ ከሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይሆናል ።

ስለሆነም አሸናፊዎች ቀደም ሲል በተገለጸው ቦታ በአካል ወይም በሕጋዊ ወኪሎቻቸው አማካኝነት ቀርበው፣ የሚጠበቅባቸውን ቅድመ-ሁኔታዎች በማሟላት በዚህ በተጠቀሰው አጭር ጊዜ ውስጥ ውል እንዲፈጽሙ የኮርፖሬሽኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ጥሪ አቅርቧል።

What's Your Reaction?

like

dislike

love

funny

angry

sad

wow