የብሪክስ (BRICS) ስብሰባ በኢራን ጉዳይ ምክንያት ያለ የጋራ ስምምነት ተጠናቀቀ!

ሎሚ ዜና ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና የተሰሙ ዋና ዋና ዜናዎች የኢራን ጦርነትና የBRICS መከፋፈል፦ በኒው ዴሊ የተካሄደው የብሪክስ (BRICS) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ፣ በኢራን ጦርነት ዙሪያ አባል ሀገራቱ መግባባት ባለመቻላቸው ያለ የጋራ መግለጫ ተጠናቋል። ኢራን እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ የሃሳብ ልዩነት አሳይተዋል።

May 16, 2026 - 11:42
 0  1
የብሪክስ (BRICS) ስብሰባ በኢራን ጉዳይ ምክንያት ያለ የጋራ ስምምነት ተጠናቀቀ!

ሎሚ ዜና ግንቦት 8 ቀን 2018 .. በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና የተሰሙ ዋና ዋና ዜናዎች የኢራን ጦርነትና BRICS መከፋፈል፦ በኒው ዴሊ የተካሄደው የብሪክስ (BRICS) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ፣ በኢራን ጦርነት ዙሪያ አባል ሀገራቱ መግባባት ባለመቻላቸው ያለ የጋራ መግለጫ ተጠናቋል። ኢራን እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ የሃሳብ ልዩነት አሳይተዋል።

 በኒው ዴሊ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ያለምንም የጋራ መግለጫ  መጠናቀቁ አሳሳቢ ሆንዋል ስብስቡ በተከታታይ ያደረጋቸው ሁለት ስብሰባዎች ያለ ስምምነት የተበተኑት በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን መካከል ባለው ጦርነት ዙሪያ ባሉ ከፍተኛ አለመግባባቶች ሳቢያ ነው።የብሪክስ ህብረት ፍላጎት አባላትን በማስፋፋት ጥንካሬ ማግኘት ቢሆንም፣ አዳዲስ አባላት የሆኑት ኢራን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) የገቡበት ቀጥተኛ ግጭት በስብስቡ ውስጥ ትልቅ መከፋፈልን  ፈጥሯል።

ሩሲያ እና ኢራን አሜሪካንበግልጽ የሚያወግዝ መግለጫ እንዲወጣ ሲገፋፉ፣ እንደ ህንድ ያሉ ሀገራት ከአሜሪካ ጋር ያላቸውን የንግድና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ላለማበላሸት ሃሳቡን ውድቅ አድርገውታል። የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ግብፅ በበኩላቸው የኢራንን የአካባቢው ሀገራት ላይ የምታደርገውን ጥቃት ኮንነዋል።በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አካባቢ ያለው አለመረጋጋት ለነዳጅ አስመጪዎቹ ቻይና እና ህንድ ትልቅ የኢኮኖሚ ስጋት ቢሆንም፣ ለችግሩ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ በፖለቲካዊ ትረካው ላይ መስማማት አልተቻለም።

 ሎሚ ዜና

#ሎሚ_ዜና #ብሪክስ #ኢራን #መካከለኛው_ምስራቅ #BRICS #IranConflict #LomiiNews

 

What's Your Reaction?

like

dislike

love

funny

angry

sad

wow