ያልተለመደው የኢቦላ ዝርያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የ88 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቱሪ ግዛት እና በአጎራባች ዩጋንዳ ድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰው አዲሱ የኢቦላ ወረርሽኝ ባልተለመደ የቫይረሱ ዝርያ የተከሰተ ከመሆኑም በላይ እስካሁን የተፈቀደ ክትባትም ሆነ ህክምና የሌለው በመሆኑ የዓለም ጤና ድርጅት ሁኔታውን “የሕዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋ” ሲል አውጇል። 

May 18, 2026 - 13:54
 0  2
ያልተለመደው የኢቦላ ዝርያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የ88 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቱሪ ግዛት እና በአጎራባች ዩጋንዳ ድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰው አዲሱ የኢቦላ ወረርሽኝ ባልተለመደ የቫይረሱ ዝርያ የተከሰተ ከመሆኑም በላይ እስካሁን የተፈቀደ ክትባትም ሆነ ህክምና የሌለው በመሆኑ የዓለም ጤና ድርጅት ሁኔታውን “የሕዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋ” ሲል አውጇል። 

የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማእከል (አፍሪካ ሲዲሲ) እንዳስታወቀው ወረርሽኙ በተመዘገበባቸው ጥቂት ቀናት ውስጥ ብቻ የ88 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፣ ሌላ 336 ሰዎች ደግሞ ቫይረሱ ሳይገኝባቸው አልቀረም ተብሎ ተጠርጥሯል። 

ይህ በእንዲህ እንዳለ ቫይረሱ ወደ ዩጋንዳ በመሻገሩ በላቦራቶሪ የተረጋገጡ ሁለት ጉዳዮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል በዋና ከተማዋ ካምፓላ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ ታውቋል።

 በአጭር ጊዜ ውስጥ እየታየ ያለው የጉዳት እና የሞት ቁጥር እጅግ አስደንጋጭ መሆኑን የገለጸው ድንበር የለሹ የሀኪሞች ቡድንም ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በብርቱ አስጠንቅቋል።

What's Your Reaction?

like

dislike

love

funny

angry

sad

wow